የኤርትራው ፕሬዚዳንት ስለ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ምን እያሉ ነው ?

ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በሀገራቸው ብቸኛው ቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ መጠይቅ #የኢትዮጵያን ስም ደጋግመው ሲያነሱ ታይተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ከወራት በፊት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በወቅቱም ኢትዮጵያ ስሟን እያነሱ ለተናገሩት ነገር ሁሉ በቀጥታ አንዳችም ምላሽ ሳትሰጣቸው በዝምታ አልፋቸዋለች።

ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱ ነበር።

በተለይም ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት።

የኢትዮጵያን የወደብ እና የባህር በር ጥያቄ " የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው " የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጣጣል ሞክረዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸውም ፕሬዝዳንቱን እንዳላስደሰተ የሚጠቁም ንግግርም ሲናገሩ ነበር።

" ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤማራት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም " በማለት " ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ " ሲሉ ተደምጠዋል።

በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት  ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም " እራሳችንን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወሳል። ነገር ግን የባህር በር ጉዳይ ህልውናዋ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አስረግጣ ተናግራለች።

ሌላው ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች (ክሱ ፦ ድንበር አካባቢ አሁንም የኤርትራ ጦር ግፍ እየፈጸመ ስለመሆኑ)  " ያሉም ሲሆን " ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲያነሱ ነበር።

ገና የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ ቢሆንም " ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ? " የሚል ንግግርም ተናግረዋል።

ሌላው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሌለባት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የማይታወቅባት ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ንግግራቸው " በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም " የሚል ንግግር አሰምተዋል።

ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ  ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን ነው ያለፈው።

ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
President Isaias Afwerki, well-known for focusing more on other nations’ affairs than his own, gave a televised interview last night on Eritrea’s only national TV station. As usual, his remarks were heavily centered on Ethiopia, with little mention of internal Eritrean matters.

This is consistent with his past behavior—where he dedicates more airtime to discussing Ethiopia and regional affairs than the problems within Eritrea.

Key Statements:
In his latest interview, Isaias once again referred to Ethiopia with dismissive and provocative language.

On Ethiopia's Demand for Access to the Sea:
He mocked and criticized Ethiopia’s efforts to gain sea access, using phrases like:

"Childish games"

"A distraction"

"A cheap lie"

"An internal cover-up"

"An expansionist agenda backed by the UAE"

He argued that Ethiopia’s request for port access is baseless and unserious.

On International Support for Ethiopia:
President Isaias appeared bothered by the growing international support Ethiopia is receiving for its Red Sea port agenda. Referring to statements from countries like France, the U.S., the UAE, and the EU, he said:

"Claiming foreign powers are with you is a sign of pressure, not a path to victory."

He followed that with a message to Ethiopians:

"Solve your internal problems first."

On Ethiopia’s Internal Conflicts:
Isaias implied that Ethiopia has lost its way politically, saying:

“The promise of reform in Ethiopia has faded.”
“There are no real political parties anymore.”

He also questioned Ethiopia’s commitment to the Pretoria Peace Agreement, which officially ended the war with Tigray.

On Eritrean Troops in Ethiopia:
Despite reports that Eritrean soldiers are still operating near the Ethiopian border, Isaias denied this, calling such claims:

“Baseless”

“Provocative”

“Part of a smear campaign”

On the Pretoria Peace Agreement:
He referenced the Pretoria deal and criticized Ethiopia for allegedly:

Not implementing it sincerely

Starting a new war with the Fano militia

Blaming Eritrea while failing to address its own internal issues

He asked:

“Why hasn’t Ethiopia implemented the Pretoria Agreement with honesty? Why are you launching new wars while claiming peace?”

On Ethiopia’s Political Structure:
He harshly criticized Ethiopia’s current political landscape:

“There’s no functioning political party in Ethiopia.”
“There’s no representative council for the people.”

Meanwhile, Isaias himself has ruled Eritrea for over 30 years without elections or opposition parties—a point many observers see as ironic given his repeated critiques of Ethiopia’s governance.

Final Takeaway:
President Isaias's comments signal renewed hostility and mistrust between Eritrea and Ethiopia, especially around:

Port access

Military involvement

Regional alliances

Political legitimacy

While Ethiopia insists it has no intention to attack any neighboring country (including Eritrea) over sea access, it continues to assert that access to the Red Sea is a matter of national survival.

Yet again, Isaias used most of his airtime not to discuss Eritrea’s internal issues but to analyze and criticize Ethiopia and other regional powers.