በነዳጅ ላይ የሚጨመር ዋጋ የለም " - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ፤ ነዳጅ እያለ ዋጋ ይጨምራል በሚል እሳቤ ' የለም ' በሚሉ ማደያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ገለጹ።
" አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ' ነዳጅ ይጨምራል ' በሚል አገልግሎት አቁመዋል። ነዳጅ ላይ የሚጨመር ዋጋ የለም " ሲሉ ለኤፍ ኤም ሲ ተናግረዋል።
መንግስት ከግንቦት ወር ጀምሮ ከነዳጅ ድጎማ መውጣቱን አመልክተዋል። የነዳጅ ዋጋም በዓለም የነዳጅ ገበያ እንደሚወሰን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ተንቀሳቅሶ እንደተመለከተው በተለያዩ የነዳጅ ማደያዎች " ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም " የሚሉ ፅሁፎች በብዛት ተለጥፎ አስተውሏል።
ነዳጅ ባለባቸው ማደያዎች ደግሞ ከፍተኛ ሰልፍ ነው ያለው።
በነዳጅ ላይ የሚጨመር ዋጋ የለም " - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) / There Is No Price Increase on Fuel” – Dr. Kassahun Gofe
