ትናንት በተሰጠው የመጀመሪያ ቀን ፈተናዎች ላይ የተወሰነ የኃይል እና የሲስተም መቆራረጥ አጋጥሞ እንደነበር የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

" ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ችግሩን በፍጥነት በመፍታት ፈተናውን ማስቀጠል ተችሏል " ሲሉ ተደምጠዋል።

" በሲስተምና በኃይል መቆራረጥ ችግር ትናንት የተሰጠውን የእንግሊዘኛ ትምህርት ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ሌሎች ትምህርቶችን ከተፈተኑ በኋላ ይፈተናሉ " ብለዋል።
Dr. Eshetu Kibede, the Director General of the Educational Assessment and Examination Services, told Ethiopian Television that there was a power and system outage during yesterday's first day of exams.

He added:
"In collaboration with the relevant stakeholders, the issue was quickly resolved, and the exam schedule continued as planned."

He further stated:
"Due to the power and system failure, students who were unable to take the English exam yesterday will sit for it after completing their other subject exams."