ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።

ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።

በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።

በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።

ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡
The Addis Ababa Revenues Bureau has announced that garlic, onion, and other unprocessed agricultural products are now exempt from Value Added Tax (VAT).

According to the Bureau, “unprocessed agricultural products consumed daily by the public are now exempt from additional VAT.”

In a circular recently issued to branch offices, the Bureau clarified that items like garlic, onion, and other similar produce are excluded from VAT when:

Imported into the country, or

Marketed domestically in their raw/unprocessed form

The exemption is based on:

VAT Proclamation No. 1341/2016, Article 10

Directive No. 570/2017 issued for its implementation

The circular states:

“Unprocessed agricultural products such as garlic, onion, and others, whether imported or locally produced and sold, are exempt from VAT.”

As a result:

Only unprocessed produce sellers are eligible for this exemption

Proper monitoring and enforcement should be carried out in relation to their use of sales registration equipment

However, the Bureau noted that fruit products are not included in this exemption. Sellers of fruit must continue applying the regular VAT system and are subject to appropriate tax audits.